የዘሜ መግለጫ ሌላ ፻ ተራሮች ኾኖ ውሏል ለካ
የዘሜ መግለጫ ሌላ ፻ ተራሮች ኾኖ ውሏል ለካ
መግለጫው የረፈረፋቸው ሁሉ አረፋ ሲደፍቁ ውለዋልና። ጥቅምት ፲ ለማለት መስከረም ፲ መባሏ serious ማወናበጃ ተደርጋ የተንታኝ ዓይነት ሳይወራጭባት አልቀረም። ወሬአቸው በሦስት ነገሮች ይፈርሳል።
፩. የዘመነ ቃል የጊዜ ጥቁምታ (Time line) አለው። በመልእክቱ የተመስገን ጥሩነህን የጥቅምት ስብሰባ ያነሣል። ተመስገን "ዘመነን አስወግደነዋል - ከእንግዲህ ድምፁን አትሰሙትም" ብሎ ባሕር ዳር ለሰበሰባቸው ካድሬዎቹ የወሸከተው ጥቅምት ከባተ ነው። መቼስ የእናንተ ጉድ አያልቅም፤ "ዘሜ ነቢዩ በመስከረም ፲ ተመስገን ጥቅምት ላይ እንደዚህ ሊንዘባዘብ እንደሚችል ተነበየ" ልትሉ ይኾናል እኮ።
ዘመነን መስከረም ፲ ላይ የአኹኑን ዓይነት መግለጫ ለመስጠት በቂ ገፊ ምክንያት አልነበረም። እንኳን እርሱ ሊናገርበት ብልጽግናዎችም ገና አላሰቡበት።
፫. አኹን በማያወላዳ ኹኔታ በራሱ አንደበት መስከረም የሚለው በጥቅምት ፲ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም. አርትዖት ተሰጥቶበታል።
አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ