የዘሜ መግለጫ ሌላ ፻ ተራሮች ኾኖ ውሏል ለካ

 





የዘሜ መግለጫ ሌላ ፻ ተራሮች ኾኖ ውሏል ለካ

መግለጫው የረፈረፋቸው ሁሉ አረፋ ሲደፍቁ ውለዋልና። ጥቅምት ፲ ለማለት መስከረም ፲ መባሏ serious ማወናበጃ ተደርጋ የተንታኝ ዓይነት ሳይወራጭባት አልቀረም። ወሬአቸው በሦስት ነገሮች ይፈርሳል።
፩. የዘመነ ቃል የጊዜ ጥቁምታ (Time line) አለው። በመልእክቱ የተመስገን ጥሩነህን የጥቅምት ስብሰባ ያነሣል። ተመስገን "ዘመነን አስወግደነዋል - ከእንግዲህ ድምፁን አትሰሙትም" ብሎ ባሕር ዳር ለሰበሰባቸው ካድሬዎቹ የወሸከተው ጥቅምት ከባተ ነው። መቼስ የእናንተ ጉድ አያልቅም፤ "ዘሜ ነቢዩ በመስከረም ፲ ተመስገን ጥቅምት ላይ እንደዚህ ሊንዘባዘብ እንደሚችል ተነበየ" ልትሉ ይኾናል እኮ።
፪. መስከረም ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም. ስለ ዘመቻ ፻ ተራሮች መግለጫ ሰጥቷል። ሞተ ተመታ ተያዘ ዓይነት ወሬ የመጣው ከተመስገን ጥሩነህ የጥቅምት ንግግር በኋላ ነው። መስከረም ፳፱ ላይ ሰሞኑን ስለዘመነ የተነዛው ኹሉ አልተባለም። እንዲያውም በመስከረም ፳፱ መግለጫው ለምን በቪድዮ አልመጣም በሚል "ቆስሏል" እያሉ የሐሰት ወሬ ነበረ ያናፈሱት።
ዘመነን መስከረም ፲ ላይ የአኹኑን ዓይነት መግለጫ ለመስጠት በቂ ገፊ ምክንያት አልነበረም። እንኳን እርሱ ሊናገርበት ብልጽግናዎችም ገና አላሰቡበት።
፫. አኹን በማያወላዳ ኹኔታ በራሱ አንደበት መስከረም የሚለው በጥቅምት ፲ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም. አርትዖት ተሰጥቶበታል።

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

የአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች በወቅታዊ ሁኔታ ላይ ለዓለም ዐቀፍ ሚዲያዎች ማብራሪያ ማቅረባቸውን አስታወቁ።

መፈክራችን ብር፣ ብር፣ ብር አሁንም ብር ነው !!!!

ሰበር ዜና - የአብይ አህመድ ልዩ ኦፕሬሽን ዝርዝር ደርሶናል